Ethiopian Reporter Magazine
Wednesday, March 29, 2023
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
Ethiopian Reporter Magazine
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
Ethiopian Reporter Magazine
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ

አስገዳጅ የነበረው የቦንድ ግዢ መመርያና አስፈሪው የኤክሳይስ ታክስ ረቂቅ አዋጅ

ሪፖርተር መጽሔት በ ሪፖርተር መጽሔት
January 2020
ውስጥ ምን ከበር አለ?
0
ያጋሩ
231
ዕይታዎች
Share on FacebookShare on Twitter

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዘጠኝ ዓመታት በፊት የግል ንግድ ባንኮችን የሚያስደነግጥ መመርያ አውጥቶ ነበር። በወቅቱ ሁሉም የግል ባንኮች ‹‹መመርያው ከሥራ ውጪ ሊያደርገን ነው›› በሚል ከፍተኛ ተቃውሞ ማሰማታቸው ይታወሳል። ብሔራዊ ባንክ ግን ባንኮቹ ባቀረቡት ተቃውሞ ላይ ምንም ዓይነት ማስተካከያም ሆነ ተጨማሪ ነገር ሳያደርግ በአቋሙ ፀና። መመርያው የግል ንግድ ባንኮች ከሚሰጡት ብድር ላይ 27 በመቶውን ለቦንድ ግዢ እንዲያውሉ የሚል አስገዳጅ መመርያ ነበር።

ባንኮቹ ያቀረቡትን ተቃውሞ በሚመለከት በወቅቱ የብሔራዊ ባንክ ገዢ የነበሩት አቶ ተክለወልድ አጥናፉ፣ ‹‹ባንኮቹ ከዚህም በላይ የቦንድ ግዢ እንዲገዙ ቢደረግ አትራፊዎች ናቸው›› የሚል ምላሽ ሰጥተው ነበር። ባንኮቹም በወቅቱ ተቃውሞ ቢያሰሙም መመርያውን ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ተግባራዊ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ምናልባትም ያገኙት የነበረው ዓመታዊ ትርፍ ከፍ ያደርግላቸው እንደነበር እንጂ፣ በዘጠኝ ዓመታት ውስጥም አትራፊ ሆነው ከርመዋል።

ባንኮቹ ከዘጠኝ ዓመት በፊት ሲያቀርቡት የነበረው ተቃውሞ የተረሳ ቢሆንም፣ ሰሞኑን ግን ባላሰቡበትና ባልተጠበቀ ሁኔታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በመመርያ እንዲተገብሩት አውጥቶት የነበረውን አስገዳጅ የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ መመርያ አንስቶላቸዋል። ባንኮቹም ከፍተኛ ደስታ ተሰምቷቸዋል። ለምን መመርያው እንደተነሳ ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፕሬዚዳንት ይናገር ደሴ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ መመርያው በመነሳቱ የግል ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረት ሳይገጥማቸው ብድር እንደ ልብ ማቅረብ ይችላሉ። በቅርቡም በቋሚነት ለሚጀመረው የመጀመርያ ደረጃ የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ላይ እንዲሳተፉ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ታስቦ መሆኑን አስረድተዋል።

የግል ባንኮቹም መመርያው በመነሳቱ፣ በብድር ወለድ ላይ የሚጥሉትን ምጣኔ ለመቀነስ መዘጋጀታቸውን (የቀነሱም አሉ) በደስታ ተናግረዋል።

በግል ባንኮች ላይ የተጣለው የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ መመርያ ሲነሳ ነጋዴውንም ሆነ ማኅበረሰቡን ያስደነገጠው ሌላ ነገር ደግሞ የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ ማሻሻያ ረቂቅ ተዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ነው። ቀድሞ የነበረውን ኤክሳይስ ታክስ አዋጅ ቁጥር 305/95 ለማሻሻል ተብሎ በገንዘብ ሚኒስቴር እንደረቀቀ የተነገረው አዲሱ ማሻሻያ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ፣ ለገቢ፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመርቷል። ረቂቅ አዋጁ ገመድ አልባ የሞባይል ኢንተርኔት ላይ ከሚጥለው አምስት በመቶ ኤክሳይስ ታክስ እስከ ትልቁ በተሽከርካሪ ላይ የጣለው 500 በመቶ ኤክሳይስ ታክስ አስደንጋጭ ሆኗል። በመሆኑም መንግሥትና የሚመለከተው አካል ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተው በዝርዝር እንዲመረምሩት ሕዝቡ እያሳሰበ ነው። አዋጁ እንዳለ ከፀደቀና ተግባራዊ የሚሆን ከሆነ፣ አዋጁን ተላልፎ የሚገኝ ነጋዴ ከ50 ሺሕ እስከ 200 ሺሕ ብር ቅጣትና ከአምስት እስከ ሰባት ዓመታት የእስር ቅጣት ይጠብቀዋል። ለማንኛውም ረቂቅ አዋጁ ውይይት ተደርጎበት እስከሚፀድቅ ድረስ፣ ነጋዴዎች የሚያስገቡት ማንኛውም ዓይነት የንግድ ዕቃ በነባሩ አዋጅ የሚስተናገድ መሆኑንና በመስገብገብ ቀደም ባለው አዋጅ መሠረት ገዝቶ በማቆየት ለመሸጥ መሞከር የሚያስቀጣ መሆኑም ተጠቁሟል።

በብዛት በመነበብ ላይ ያሉ መጣጥፎች

ዶ/ር ቅድስት

“አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

May 2020
C:\Users\IT\Documents\A01\pics

የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

July 2020
የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

May 2020
ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

May 2020
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ

ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

May 2020

Follow us on Facebook

  • ዶ/ር ቅድስት

    “አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

    384 shares
    Share 384 Tweet 0
  • የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

    21 shares
    Share 21 Tweet 0
  • የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

    0 shares
    Share 0 Tweet 0
  • ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

    44 shares
    Share 44 Tweet 0
  • ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

    169 shares
    Share 169 Tweet 0
Ethiopian Reporter Magazine

ሪፖርተር ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር

(+251) 116 61 61 81

(+251) 116 61 61 85

[email protected]

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተመ የሚወጣ ወርኃዊ መጽሔት ሲሆን፣ የሚያተኩረውም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

ሪፖርተር መጽሔት በ ኢሜይል ለማግኘት

  • Ethiopian Reporter
  • The Reporter Ethiopia
  • Reporter Tenders
  • Ethiopian Reporter Jobs

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • የፊት ገጽ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

Login to your account below

Forgotten Password?

Fill the forms bellow to register

All fields are required. Log In

Retrieve your password

Please enter your username or email address to reset your password.

Log In