Ethiopian Reporter Magazine
Wednesday, March 29, 2023
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
Ethiopian Reporter Magazine
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
Ethiopian Reporter Magazine
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ

መፍትሔ ያልተገኘላቸው የታገቱ የደንቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች

ሪፖርተር መጽሔት በ ሪፖርተር መጽሔት
February 2020
ውስጥ ምን ከበር አለ?
0
ያጋሩ
405
ዕይታዎች
Share on FacebookShare on Twitter

ከታገቱ ሁለት ወራት ያለፋቸው የደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጉዳይ ወላጆቻቸውን ብቻ ሳይሆን መላው ኢትዩጵያውያንን ማስጨነቁ ቀጥሏል። የተወሰኑ ታጋች ተማሪዎች ወላጆች ወደ አዲስ አበባ ጥሪ ተደርጒላቸው መምጣታቸው ሲሰማ፤ የተለያየ ግምት ተሰጥቶ ነበር። ስለተማሪዎቹ መታገት በተለያዩ ድረ-ገጾች አስደንጋጭና ተስፋ አስቆራጭ መረጃ ይተላለፍ ስለነበር፤ቤተሰቦቻቸው በመንግስት ደረጃ መጠራታቸው ሲሰማ፤ በድረገጾች የተላለፈው አስደንጋጭ መረጃ ትክክለኛነትም እስከማረጋግጥ የተደረሰ ቢሆንም ውጤቱ ግን ሌላ ሆኗል። የታገቱ የተወሰኑ ተማሪዎች ቤተሰቦች አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ የተገናኙት ከምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን ጋር ነው። ወላጆቹ ከልጆቻቸው መገናጀት ካቋረጡበት ጊዜ አንስትው በጭንቀት ላይ መሆናቸውን ተናግረው፤ መንግስት የልጆቻቸውን ሕይወት እንዲታገድላቸው ጠይቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድን ጨምሮ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የሰላም ሚኒስትሯ ሙፈሪያት ካሚልና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች እነዲሁም ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ የተማሪዎቹ የትውልድ ቦታ ተወካዮች ከታገቱ የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወላጆች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።ወላጆች የልጆቻቸው አድራሻ እስከጠፋበት ዕለት ድረስ የነበራቸው የስልክ ልውውጥ ምን እንደሚመስልም ጉዳዩን በሚመለከት ለተቋቋመውና በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ለሚመራው ግብረ-ሃይልን መናገራቸውም ተነግሯል።

ግብረ-ሃይሉን የሚመሩት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን መንግስት የታገቱ ተማሪዎችን ለማስፈታት እያከናወነው ያለውን ተግባር ለወላጆቹ እንዳብራሩላቸው፤ በተማሪዎቹ ላይ ጉዳት እንደደረሰ የሚያሳይ የተረጋገጠ መረጃም ሆነ ማስረጃ አለመኖሩንና ከወላጆቹ ጋ ለቀጣይ ስራ የሚሆን መረጃ መገኘቱንም ገልጸዋል ተብሏል።

መንግስት ተማሪዎቹን ለማስለቀቅ ሲባል በጥንቃቄና አስተውሎት እየሰራ መሆኑንና ችግሩን ለመፍታት ወላጆች በምን መልኩ መንቀሳቀስ እንዳለባቸውም ጭምር ምክክር መደረጉተጠቁሟል። የጸጥታ መዋቅሩና የፖለቲካ አመራሩ፤ ተማሪዎችን ለማስለቀቅ ያለምንም እረፍት እየሰራ መሆኑም አንደተገለጸ ታውቋል።

ሁሉም የታገቱት ተማሪዎች 17 እንደሆኑና ሁሉም የአራማ ክልል ተማሪዎች መሆናቸው ሲነገር የቆየና ዘርን መሠረት ያደረገ እገታ እንደሆነ ቢገለጽም መንግስት ግን አስተባብሏል። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬትሪያት አቶ ንጉሱ ጥላሁን ቀደም ብለው በሰጡት መግለጫ፤ የታገቱት ተማሪዎች 17 ሳይሆኑ ከዛበላይ መሆናቸውን ጠቁመው 21 ተማሪዎችን በድርድር ማስመለስ መቻሉንና ስድስት ተማሪዎች ብቻ እንደቀሩ መግለጻቸው ይታወሳል። አቶ ንጉሱ መግለጫውን ከሰጡ በኋላ ተለቀዋል የተባሉት ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ጋር አልተገናኙም።ወይም ወደ ዩኒቨርሲቲው መመለስ ባለመቻላቸው “ተማሪዎቹ የታሉ? ተማሪዎቻችንን መልሱ፤ አስመልሱና መንግስት ግልጽ መረጃ ይስጥ” የሚሉ ተቃውሞዎች በድረ ገጾችና በሰላማዊ ስልፎች ጭምር ሲቀርቡ ከርመዋል። ስለታገቱ ተማሪዎች ጥያቄውና ተቃዉሞው እስከ ሰላማዊ ሰልፍ ደርሷል። ሰላማዊ ሰልፉም በአማራ ክልል በባህር ዳር፤ ጎንደር፣ደብረብርሀን፤ በደብረ ማርቆስና በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች በተደረገ ሰላማዊ ሰልፍ መንግስት ስለታገቱት ተማሪዎች ግልጽ መረጃ እንዲሰጥ ተጠይቋል። ሰላማዊ ሰልፉ እንደተደረገ የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪ አቶ ንጉሱ ጥላሁን፣የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል እንዳሻው ጣሰውና የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) መግለጫ ሰጥተዋል። ኃላፊዎቹ “እገታው የብሄር መልክ የለውም” ካሉ በኋላ፤ ቀደም ብሎ የተነገረውን የታገቱ የዩኒቨርሲ የተማሪዎች ቁጥር 14 መሆኑንና አምስት የአካባቢውነዋሪዎች በድምሩ 19 መሆናቸውን በመግለጽ ሁሉንም ግር ያሰኘ መረጃ ሰጥተዋል። ከሶስት ሳምንታት በፊት 21 ተማሪዎች ስመለቀቃቸውና ስድስት ተማሪዎች ስለመቅረታቸው የተነገረው መረጃ ተትቶ 14 ተማሪዎች እንደታገቱና አምስት ደግሞ ሌሎች ሰዎች መሆናቸውን በመገለጹ፤ የሁሉም ጭንቀትና ጥርጣሬው ቀጥሏል።

የፌዴራል ፖሊስ የምርመራ ቡድን አቋቁሞ ክትትል እያደረገ መሆኑን፤ የታገቱት ተማሪዎች የደረሰበቸው ጉዳት ስለመኖሩ መረጃ እንደሌለውና በአጠቃላይ በአካባቢው ያለውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት የፀጥታ ኃይሎች ተባብረው እየሰሩ መሆኑን ኃላፊዎቹ ገልፀዋል። የመንግስት ኃላፊዎች መግለጫውን ከሰጡ በኋላ ስለተማሪዎቹ እገታ ያለው ጭንቀት ጨምሯል። መንግስት ያለውን አስቸጋሪም ይሁን ጥሩ ነገር ሳያቅማማ በግልጽ ሊናገር ይገባል የሚል ተቃውሞም መሰማቱ ቀጥሏል።

በብዛት በመነበብ ላይ ያሉ መጣጥፎች

ዶ/ር ቅድስት

“አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

May 2020
C:\Users\IT\Documents\A01\pics

የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

July 2020
የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

May 2020
ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

May 2020
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ

ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

May 2020

Follow us on Facebook

  • ዶ/ር ቅድስት

    “አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

    384 shares
    Share 384 Tweet 0
  • የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

    21 shares
    Share 21 Tweet 0
  • የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

    0 shares
    Share 0 Tweet 0
  • ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

    44 shares
    Share 44 Tweet 0
  • ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

    169 shares
    Share 169 Tweet 0
Ethiopian Reporter Magazine

ሪፖርተር ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር

(+251) 116 61 61 81

(+251) 116 61 61 85

[email protected]

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተመ የሚወጣ ወርኃዊ መጽሔት ሲሆን፣ የሚያተኩረውም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

ሪፖርተር መጽሔት በ ኢሜይል ለማግኘት

  • Ethiopian Reporter
  • The Reporter Ethiopia
  • Reporter Tenders
  • Ethiopian Reporter Jobs

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • የፊት ገጽ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

Login to your account below

Forgotten Password?

Fill the forms bellow to register

All fields are required. Log In

Retrieve your password

Please enter your username or email address to reset your password.

Log In