Ethiopian Reporter Magazine
Wednesday, March 29, 2023
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
Ethiopian Reporter Magazine
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
Ethiopian Reporter Magazine
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ

የስፖርት ውድድሮችን ያዘጋው የኮሮና ወረርሽኝ

በ ደረጀ ጠገናው
April 2020
የስፖርት ውድድሮችን ያዘጋው የኮሮና ወረርሽኝ
0
ያጋሩ
414
ዕይታዎች
Share on FacebookShare on Twitter

በማይታመን ፍጥነት ዓለምን እያዳረሰ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት በርካታ ስፖርቶች እንዲቋረጡ ተደርጓል፣ አንዳንዶቹ ደግሞ ለሌላ ጊዜ ተላልፏል፡፡ የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ዙሪያ ከ34,000 በላይ ሰዎችን ለኅልፈት ዳርጓል፡፡ ኮቪድ-19 የሚል ተቀፅላ ያለው በሽታው ከ735,000 በላይ ሰዎችን አጥቅቷል፡፡

መንግሥታት ወረርሽኙን ለማቆም የተለያዩ ዕርምጃዎች እየወሰዱ ይገኛሉ፡፡ ሕዝብ በየቦታው እንዳይሰባሰብ፣ እንዳይጨባበጥ ግዴታም መልዕክትም እያሠራጩ ነው፡፡

ብርሃኑ ለገሰ ያሸነፈበትና የካቲት 23 የተካሄደው የቶኪዮ ማራቶን ተወዳዳሪዎች ከዓምናው ያነሱት በኮረና ቫይረስ ምክንያት ነው

 ከታላላቅ መግለጫዎች መካከል የኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ኮሚቴ (አይኦሲ) እና የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንሁ አቤ የቶኪዮ 2020 ኦሊምፒክ ዘንድሮ ከሐምሌ 17 ቀን ጀምሮ ለማካሄድ የተያዘውን ፕሮግራም በመሰረዝ ለሚቀጥለው ዓመት እንዲካሄድ መስማማታቸው ነው፡፡ አይኦሲ መጋቢት 21 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ እንዳደረገው የ2020 ኦሊምፒክ ከዓርብ ሐምሌ 16 ቀን 2013 ዓ.ም. እስከ እሑድ ነሐሴ 2 ቀን እንዲካሄድ ወስኗል፡፡

በሌላ በኩል በሰሜን አሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶኮር፣ ብሔራዊ የቅርጫት ኳስ ማኅበርና ብሔራዊ ሆኪ ሊግ ውድድሮች እንዳይካሄዱ አግደዋል፡፡ በአውሮፓ በቫይረሱ ክፉኛ የተጠቃችው ጣሊያንም ሁሉንም ስፖርታዊ ኩነቶች ዘግታለች፡፡

ተዛማጅ ጽሑፎች

አዲሱ የአኖካ ዞናዊ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ (ዶ/ር)

May 2021
ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

March 2020

በየአራት ዓመቱ እንዲካሄድ ምክረ ሐሳብ የቀረበበት የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ

February 2020

ከሃምሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ዘንድሮ በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስሙ የነገሠው አበበ ቢቂላ

January 2020

እግር ኳስ

በመጪው ሚያዝያ በካሜሩን አዘጋጅነት ሊካሄድ የነበረው የ2020 አፍሪካ ዋንጫ ለቀጣዩ ዓመት እንዲተላለፍ አኅጉራዊው ኮንፌዴሬሽን ወስዷል፡፡ በደቡብ አሜሪካ ፉትቦል ኮንፌዴሬሽን የሚዘጋጀው ኮፓ አሜሪካም እንዲሁ ለቀጣይ ዓመት አስተላልፎታል፡፡ በተመሳሳይም የአውሮፓ እግር ኳስ ማኅበር የዘንድሮውን የአውሮፓ ዋንጫ ለ2021 አስተላልፏል፡፡

ማራቶን

በዓለም አትሌቲክስ ዕውቅና ያላቸው የለንደንና የቦስተን ማራቶች ውድድር ወደ መስከረም 2013 ዓ.ም. ሲተላለፉ፣ የአምስተርዳም፣ ፓሪሰና ባርሴሎና ማራቶኖችም ተመሳሳይ ዕርምጃ ወስደዋል፡፡ የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ለቀጣይ ዓመት ከተላለፉት ውስጥ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ምላሽ

ኮሮና ካሰናከላቸው ስፖርቶች ኢትዮጵያውያኑ የሚታወቁበት አትሌቲክስ ዋነኛው ነው፡፡ የማናጀር ተወካይና አሠልጣኝ እንዲሁም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የብሔራዊ አትሌቶች አሠልጣኝ የሆኑት አቶ ሐጂ አዴሎ እንደሚገልጹት፣ ኮሮና አሁን ባለው ሁኔታ አደገኛና ዓለምን ትልቅ ሥጋት ውስጥ ያስገባ ቫይረስ ሆኗል፡፡

አሠልጣኙ ከ100 በላይ ታዋቂና ጀማሪ አትሌቶች በሥራቸው ይገኛሉ፡፡ አትሌቲክስ በባህሪው ለአንድ ውድድር ብቻ አራትና ከዚያም በላይ የዝግጅት ጊዜ የሚጠይቀውን ያህል ከፍተኛ የሆነ ላብ የሚያስወጣ የስፖርት ዓይነት መሆኑን የሚናገሩት አሠልጣኝ ሐጅ፣ ይህ ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ከየትኛውም አገር በተለየ ለኢትዮጵያውያን ከባድ እንደሚሆን ይናገራሉ፡፡ ምክንያቱንም ሲያስረዱ፣ “የሩጫ ውድድር ውጤት የሚያስገኘው ከብዙ ድካምና ልፋት በኋላ ያውም ዕድለኛ ለሚሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ደግሞ ሁሉም እንደሚያውቀው አንዳንዶቹ የቀን ሥራ እየሠሩ ነገን ተስፋ አድርገው የሚሠሩ ምንም ዓይነት ወርኃዊ ገቢ የሌላቸው በመሆኑ ጉዳቱ ሕይወትን ከማሳጣት በተጨማሪ በጥቅማ ጥቅም ደረጃም ነው” በማለት የሚኖረውን ተፅዕኖ ያስረዳሉ፡፡

በሥነ ልቦናው ረገድም ቢሆን አትሌቶች ላይ እያሳደረ ያለው ተፅዕኖ  ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ በዚህ የሚስማሙት አሠልጣኙ፣ ‹‹አትሌቶቻችን የሚያጡት ነገር እንደተጠበቀ ሆኖ ችግሩ የመላው ዓለም በመሆኑ መቅደም ላለበት የሰው ልጆች ሕይወት ስለሆነ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ነው እየሠራን የምንገኘው፡፡ ቫይረሱ ከተከሰተ ማግሥት ጀምሮ አትሌቶች ጥቅም የሚያገኙባቸው የተለያዩ በርካታ ውድድሮች ተሰርዘዋል፡፡ በግሌ እንደ አሠልጣኝና ማናጀር የሚሰማኝ ይኖራል፣ ይሁን እንጂ አሁን ቅድሚያ መስጠት የሚጠበቅብን ለሰው ልጆች ጤና ነው፣ አትሌቶቹ ይህን ክስተት ማለፍ ከቻሉ ብዙ ነገር ከፊት ለፊታቸው የሚጠብቃቸው እንደመሆኑ ያንን አስበው ሊንቀሳቀሱ ይጋባል፤›› በማለት ይመክራሉ፡፡

ለወትሮ በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ተራራማና ጫካማ ሥፍራዎች ጠዋትና ከሰዓት እጅብ ብለው ልምምድ የሚሠሩ አትሌቶች እነዚያ ሮጠው የማይጠግቡ እግሮቻቸው ተጣጥፈው ከቤት እንዲውሉ አስገድዷቸዋል፡፡

አሠልጣኝ ሐጅ፣ ወረርሽኙ ምንም እንኳ ከሰዎች ወደ ሰዎች የሚተላለፍበት አንዱና ዋናው ንክኪ እንደሆነ ቢታመንም በጥንቃቄ የተናጠል ልምምዶችን መሥራት እንደሚያስፈልግ ያምናሉ፡፡ በእርግጥ ኮሮና መቼና በምን ያህል ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ሥር እንደሚውል አሁን ከፈጣሪ ውጪ የሚያውቅ እንደሌለ የሚናገሩት አሠልጣኙ፣ ‹‹ቫይረሱ መፍትሔ ቢገኝለት እንኳ ቀደም ሲል ወደነበረው ዓይነት ፕሮግራሙን ለማስተካከል ከባድ ነው፡፡ ምክንያቱም ውድድር አዘጋጅ አገሮችና ስፖንሰር አድራጊ ኩባንያዎችና ድርጅቶች በቫይረሱ ምክንያት ኢኮኖሚያቸው በከፍተኛ ኪሳራ ውስጥ የገባባቸው በርካታ ናቸው፡፡ አትሌቲክስ ደግሞ ከሌሎች ስፖርቶች በተለየ በስፖንሰሮች አማካይነት የሚንቀሳቀስ ዘርፍ ነው፡፡ ስፖርቱ ወደ ነበረበት ለመመለስ በተለይ በዚህ ቀውስ ኢኮኖሚያቸው ጉዳት የደረሰበት ኩባንያዎችና ድርጅቶች ጊዜ የሚፈልጉ በመሆኑ በግሌ ለአትሌቲክሱ ትልቁ ጉዳት ይህ ነው የሚመስለኝ፤›› በማለት አትሌቲክሱ በሒደት ስለሚገጥመው ፈተና ሥጋታቸውን ያስቀምጣሉ፡፡

ኮሮና ቫይረስ ባይከሰት ኖሮ አንዳንዶቹ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይህ ወቅት ዓለም ላይ በወርቅ ደረጃ በሚመደቡ የጎዳና ላይ ውድድሮች ውስጥ እንደ ቦስተንና ለንደን ማራቶኖች እንዲሳተፉ የሚደረገው የመግቢያ ተከፍሏቸው ነው፡፡ አትሌቶቹ ውድድሩን አሸንፈው ከሚያገኙት በላይ ለመግቢያ ብቻ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዶላሮች ማግኘት የሚችሉባቸው እንደሆኑ የሚናገሩት አሠልጣኝ ሐጅ፣ ‹‹ሁለቱም ውድድሮች እንዲተላለፉ ሲወሰን የሚደረጉበት ወቅትም ተቀራራቢ ነው፣ ሥጋቱ አንዱና ዋነኛው እንደዚህ ውድድሮች ሲደራረቡ አትሌቶች የሚያገኟቸውን ጥቅሞች ያጣሉ፡፡ ከአትሌቶች ባሻገር ለዋናው አወዳዳሪ አካል የዓለም አትሌቲክስ ማኅበር ጭምር ትልቅ ራስ ምታት መሆኑ የማይቀር ነው፤›› በማለት የችግሩን ግዝፈት ያስረዳሉ፡፡

የኮሮና ቫይረስ በዚህ መልኩ መከሰት ሌላው ችግር ሲሉ የሚያስረዱት አሠልጣኙ፣ ‹‹እኔን ጨምሮ ብዙዎቹ የዘርፉ ሙያተኞች የተለመደውን የዕለት ዕለት ሥራ እየሠራን ነው ለማለት የሚያስደፍር አይደለም፡፡ ወጥተን የምንገባው በከፍተኛ ሥጋት ውስጥ ሆነን ነው፡፡ በአትሌቶቹ መካከል ከፍተኛ የሆነ መፈራራትና መጠራጠር ይስተዋላል፣ ማናጀሮችና ውድድር አዘጋጆች እስካሁን ባለው አንዳቸውም በስፖርቱ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ መናገር አይፈልጉም፣ ሁሉም ቅድሚያ ለአትሌቶቻችን ጤንነት ትኩረት እንድንሰጥ ብቻ ነው፤›› በማለት አሁን ላይ የስፖርቱን የወደፊት ዕጣ በሚመለከት የሚናገሩት አንዳችም እንደሌለ ያስረዳሉ፡፡

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ትልቅ ታሪክ ካላቸው ቀደምቶች መካከል አንዱ ነው፡፡ በኦሊምፒክና በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናና ከሁለት አሠርታት በላይ ቆይታው የዓለም አዳዲስ ክብረ ወሰኖች በእጁ ጨብጧል፡፡ ከአዲስ አበባ 175 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኘው የአሰላ ከተማ አቅራቢያ ከምትገኝ የገጠር ቀበሌ ተነስቶ በአሁኑ ወቅት ከባለ ቢሊየነሮች ተርታ የሚመደበው ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ኮሮና ቫይረስ ለኢትዮጵያውያን አትሌት የሚኖረውን ተፅዕኖ አስመልክቶ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርጓል፡፡

በአሁኑ ወቅት ዓለም እያተራመሰ የሚገኘው ኮሮና ቫይረስ አሁን በያዘው መልኩ የሚቀጥል ከሆነ በሰው ልጆች ሕይወት ላይ የሚያስከትለው ጉዳት እንደተጠበቀ፣ በተለይ ለወጣት አትሌቶች የወደፊት ዕጣ ከባድ እንደሚያደርግባቸው ቅድመ ግምቱን አስቀምጧል፡፡

አትሌቲክስ በተለይም የጎዳና ላይ ውድድሮች ከመቼውም ጊዜ በተሻለ የአትሌቶችን ሕይወት የሚቀይሩ እየሆኑ በሚገኝበት በአሁኑ ወቅት፣ ወጣትና ተተኪ አትሌቶች በዚህ እጅግ አስፈሪ በሆነ ወረርሽኝ ሲበላሽ መመልከት ከባድ ቢሆንም፣ በሕይወት መኖር ካልተቻለ ሁሉም ነገር ስለሚቀር በተለይ ወጣት አትሌቶች ነገሮችን በትዕግሥት ማለፍ እንደሚጠበቅባቸዋል ይመክራል፡፡

ShareTweetShare

ተዛማጅ Posts

አዲሱ የአኖካ ዞናዊ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ (ዶ/ር)
ስፖርት

በ ሔኖክ ያሬድ
May 2021
0

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር- የዞን አምስት (አኖካ ዞን 5) ፕሬዚዳንት ሆነው በከፍተኛ ድምፅ ተመረጡ፡፡ አኖካ ዞን-5 በክፍለ አኅጉሩ የሚገኙ አሥራ...

ተጨማሪ ያንብቡ
ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

March 2020
በየአራት ዓመቱ እንዲካሄድ ምክረ ሐሳብ የቀረበበት የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ

በየአራት ዓመቱ እንዲካሄድ ምክረ ሐሳብ የቀረበበት የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ

February 2020
አበበ ቢቂላ

ከሃምሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ዘንድሮ በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስሙ የነገሠው አበበ ቢቂላ

January 2020

በብዛት በመነበብ ላይ ያሉ መጣጥፎች

ዶ/ር ቅድስት

“አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

May 2020
C:\Users\IT\Documents\A01\pics

የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

July 2020
የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

May 2020
ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

May 2020
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ

ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

May 2020

Follow us on Facebook

  • ዶ/ር ቅድስት

    “አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

    384 shares
    Share 384 Tweet 0
  • የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

    21 shares
    Share 21 Tweet 0
  • የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

    0 shares
    Share 0 Tweet 0
  • ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

    44 shares
    Share 44 Tweet 0
  • ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

    169 shares
    Share 169 Tweet 0
Ethiopian Reporter Magazine

ሪፖርተር ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር

(+251) 116 61 61 81

(+251) 116 61 61 85

[email protected]

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተመ የሚወጣ ወርኃዊ መጽሔት ሲሆን፣ የሚያተኩረውም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

ሪፖርተር መጽሔት በ ኢሜይል ለማግኘት

  • Ethiopian Reporter
  • The Reporter Ethiopia
  • Reporter Tenders
  • Ethiopian Reporter Jobs

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • የፊት ገጽ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

Login to your account below

Forgotten Password?

Fill the forms bellow to register

All fields are required. Log In

Retrieve your password

Please enter your username or email address to reset your password.

Log In