Ethiopian Reporter Magazine
Wednesday, March 29, 2023
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
Ethiopian Reporter Magazine
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
Ethiopian Reporter Magazine
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ

ምክሮችንና መመሪያዎችን  ከመስማት ባለፈ መተግበር  ግዴታ ነው!

ሪፖርተር መጽሔት በ ሪፖርተር መጽሔት
April 2020
0
ያጋሩ
866
ዕይታዎች
Share on FacebookShare on Twitter

እ.አ.አ በታህሣሥ ወር 2019 መጨረሻ ላይ በቻይና አገር ሁቤ ግዛት ውሀን ከተማ የተነሳው ኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ወረርሽኝ፤ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ሁኔታ ዓለምን በፍጥነት አዳርሷል፡፡  ወረርሽኙ ከአንዱ ወደ ሌላው መተላለፍና መዛመት ብቻ ሳይሆን ገዳይነቱም ፈጣን ነው፡፡ ወረርሽኙ በሶስት ወራት ውስጥ በመላው ዓለም ከ6ዐዐ ሺህ በላይ ሰዎችን አጥቅቷል፡፡ ከ3ዐ ሺህ በላይም የሚሆኑ ሰዎችም ህይወታቸው አልፏል፡፡ ቫይረሱ እንዳለባቸው ከተረጋገጠባቸው በኋላ ማገገም የቻሉት ከ134 ሺህ በላይ መሆናቸውንም እስከ መጋቢት 21 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም የወጡ ዓለም አቀፍ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ 

ዜጐቻቸው በብዛት ከሞቱባቸው መካከል ከፍተኛውን ቁጥር ያስመዘገቡት ከአውሮፓ አገሮች ውስጥ ጣሊያንና እስፔን ናቸው፡፡  ጣሊያን ከ1ዐ ሺህ በላይ፤ እስፔን ደግሞ ከ5 ሺህ በላይ ዜጐቻቸው ሞተውባቸዋል፡፡ ወረርሽኙ የተነሳባት ቻይና 81 394 ዜጐቿ በወረርሽኙ ተጠቅተውባት የነበረ ሲሆን 3,295ቱ ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል፡፡ ወረርሽኙ በከፍተኛ ፍጥነት እተዛመተባትና  በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ11ዐ ሺህ በላይ ዜጐቿ በቫይረሱ መጠቃታቸው የታወቀው አሜሪካ ስትሆን ከ2ዐዐዐ በላይ የሚሆኑ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ ወረርሽኙ በ47 አፍሪካም አገራት የተሠራጨ ሲሆን እስከ መጋቢት 21 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም ድረስ ከ3,800 በላይ ዜጎች  በቫይረሱ የተጠቁ ሲሆን የሟቾችም ቁጥር 110 ደርሷል፡፡  በአልጄሪያ ከ25 በላይና በግብፅ ከ24 በላይ ሰዎች ሞተዋል፡፡ ከአፍሪካ ሀገሮች ከ1100 በላይ ዜጎቿ በቫይረሱ የተጠቁባት ሀገር ደቡብ አፍሪካ ስትሆን፤ ግብጽና አልጀሪያም ከ456 እና ከ367 በላይ ዜጎቻቸው ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡ ሌሎቹም የአፍሪካ አገራት ዜጎቻቸው በወረርሽኙ እየተጠቁና በሞት እየተነጠቁ ይገኛል፡፡  ይህ ሁሉ የሆነው ግን በበሶስት ወራት ውስጥ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የዜጐች ከፍተኛ የሆነ ማህበራዊ ቅርርብ ያላቸው በመሆኑ ማለትም በከፍተኛ ቅርርብና መጨባበጥ ሠላምታ መለዋወጥ፤ሲያስነጥሱ ጥንቃቄ አለማድረግ እንዲሁም እጅን በአግባቡ አለመታጠብ ናቸው፡፡

ኢትዮጵያም ዜጐቻቸው በቫይረሱ ከተጠቁባቸው አገሮች መካከል አንዷ ናት፡፡ ምንም እንኳን ሞት ያልተመዘገበባት እና የተጠቂ ሰዎች ቁጥር እስከ መጋቢት 21 ቀን 2ዐ1ዐ ዓ.ም ድረስ 21 ብቻ ቢሆንም፤ ከፍተኛ የሆነ ጥንቃቄ ያስፈልጋታል፡፡ መንግስና የጤና ባለሙያዎች በተደጋጋሚ የሚያስተላልፉትን ምከርና መመሪያ መፈፀም ለህይወት ዋስትና መስጠትና ወገኖችን መታደግም ጭምርም ነው፡፡ ምንም እንኳን ማህበራዊ ግንኙነቶች እጅግ የተወሳሰቡ፣ ሁሉንም ነገር ተነካክቶና ተጠጋግቶ የመፈፀም ልምድ ቢኖርም፤ አሁን ላይ ግን አካላዊ ርቀትን (Physical Distance) መጠበቅ ግድ ይላል፡፡ በመተላለፊያ መንገዶች፣ ትራንስፖርት መጠበቂያ ቦታዎችና ፌርማታዎች፣ በርካታ ሰዎች የሚገናኙባቸው አደባባዮች፣ በተለይም በቤተ አምልኮ ስፍራዎች(የቤተክርስቲያናት ቅጥር ጊቢ) ያለው መጠጋጋትና እየተገፋፉ መንቀሳቀስ ያልቀረበት ሁኔታ ስላለ፤በራሳቸው እንዲያስተካክሉ ውይም ያ የማይሆን ከሆነ የመንግስት መመሪያን አስፈፃሚ አካላት እርምጃ በመውሰድ የማስፈጸም ግዴታ አለባቸው፡፡ ምክንያቱም ከአቅም በላይ የሆነና ሕዝብን አደጋ ላይ የሚጥል ነገር ሲያጋጥም አስፈላጊውን እርምጃ ወስዶ ማዳን ኃላፊነት አለበት፡፡

ሕዝብን የማዳን ኃላፊነት የመንግስት ከመሆኑ አንፃር፤ ለሕዝቡ ደህንነት ሲባል ያወጣውን መመሪያ መተግበር ደግሞ የሕዝቡ ኃላፊነት መሆኑን ማወቅም ያስፈልጋል፡፡  ወረርሽኙን መከላከልና መግታት የሚቻለው፤ በጤና ባለሙያዎች የሚነገሩትን ወይም የሚተላለፉትን የጥንቃቄ መንገዶች መፍትሄዎች ማለትም በቤት ውስጥ በመቀመጥ፣ እጅን አዘውትሮ በመታጠብ፣ የአካል ርቀትን በመጠበቅ(Phisical Distance)፣ ባለመጨባበጥና የመንግሥትን መመሪያ በተግባር ላይ በማዋል ብቻ በመሆኑ; እነዚህን ተግባራት መፈፀም ግዴታም ጭምር ነው!

ተዛማጅ ጽሑፎች

ፈታኝ ጊዜያትን ለማለፍ ጥንቃቄና ብልሃትን መሣሪያ ማድረግ ግድ ይላል

ፈታኝ ጊዜያትን ለማለፍ ጥንቃቄና ብልሃትን መሣሪያ ማድረግ ግድ ይላል!

May 2020
Ethiopian Reporter Magazine based in Addis Ababa, Ethiopia

“ ኢትዮጵያ በሉዓላዊነቷ ላይ ከማንም ጋር አትደራደርም !!”

March 2020

“ስለልጆች የማይገደው መንግስት አባት አይባልም !”

February 2020

መጪው ምርጫ  ምርጫ እንዳያሳጣን!

January 2020

ተዛማጅ Posts

ፈታኝ ጊዜያትን ለማለፍ ጥንቃቄና ብልሃትን መሣሪያ ማድረግ ግድ ይላል
ከሪፖርተር

ፈታኝ ጊዜያትን ለማለፍ ጥንቃቄና ብልሃትን መሣሪያ ማድረግ ግድ ይላል!

በ ሪፖርተር መጽሔት
May 2020
0

ዓለም በ21ኛው ክፍለ ዘመን ፈተናዋ በዝቷል፡፡ የእርስ በርስ ጦርነት፣ መጐዳዳት፣ መገዳደል፣ ስደት፣ መፈናቀል፣ ድርቅ፣ የአየር ንብረት መቀያየር፣ በአገሮች መካከል ከቃላት ጦርነት ጀምሮ በጦር መሣሪያ የታገዘ ውጊያ ማድረግ የዕለት ተዕለት...

ተጨማሪ ያንብቡ
Ethiopian Reporter Magazine based in Addis Ababa, Ethiopia

“ ኢትዮጵያ በሉዓላዊነቷ ላይ ከማንም ጋር አትደራደርም !!”

March 2020
Ethiopian Reporter Magazine based in Addis Ababa, Ethiopia

“ስለልጆች የማይገደው መንግስት አባት አይባልም !”

February 2020
Ethiopian Reporter Magazine based in Addis Ababa, Ethiopia

መጪው ምርጫ  ምርጫ እንዳያሳጣን!

January 2020

በብዛት በመነበብ ላይ ያሉ መጣጥፎች

ዶ/ር ቅድስት

“አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

May 2020
C:\Users\IT\Documents\A01\pics

የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

July 2020
የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

May 2020
ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

May 2020
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ

ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

May 2020

Follow us on Facebook

  • ዶ/ር ቅድስት

    “አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

    384 shares
    Share 384 Tweet 0
  • የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

    21 shares
    Share 21 Tweet 0
  • የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

    0 shares
    Share 0 Tweet 0
  • ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

    44 shares
    Share 44 Tweet 0
  • ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

    169 shares
    Share 169 Tweet 0
Ethiopian Reporter Magazine

ሪፖርተር ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር

(+251) 116 61 61 81

(+251) 116 61 61 85

[email protected]

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተመ የሚወጣ ወርኃዊ መጽሔት ሲሆን፣ የሚያተኩረውም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

ሪፖርተር መጽሔት በ ኢሜይል ለማግኘት

  • Ethiopian Reporter
  • The Reporter Ethiopia
  • Reporter Tenders
  • Ethiopian Reporter Jobs

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • የፊት ገጽ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

Login to your account below

Forgotten Password?

Fill the forms bellow to register

All fields are required. Log In

Retrieve your password

Please enter your username or email address to reset your password.

Log In