Ethiopian Reporter Magazine
Wednesday, March 29, 2023
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
Ethiopian Reporter Magazine
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
Ethiopian Reporter Magazine
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ

መንግሥትንና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን እያወዛገበ ያለው አገር አቀፍ ምርጫ

በ ሪፖርተር መጽሔት
May 2020
መንግሥትንና-ተፎካካሪ-ፓርቲዎችን-እያወዛገበ-ያለው-አገር-አቀፍ-ምርጫ

መንግሥትንና-ተፎካካሪ-ፓርቲዎችን-እያወዛገበ-ያለው-አገር-አቀፍ-ምርጫ

1
ያጋሩ
465
ዕይታዎች
Share on FacebookShare on Twitter

ከአምስት ዓመታት በፊት በ2ዐዐ7 ዓ.ም. በተደረገው አምስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ፣ መቶ በመቶ አሸናፊ የነበረው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞከራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) አንድ ዓመት እንኳን ሳይሞላው ከሁለት ጊዜ በላይ ካቢኔውን ቢቀያይርም አገሪቱን በተረጋጋ ሁኔታ መምራት ባለመቻሉ የበላይ አመራሩ በ2ዐ1ዐ ዓ.ም. መጋቢት ወር መገባደጃ ላይ ተቀይሯል፡፡ 

በአምስተኛው አገራዊ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስትር ተደርገው የተሾሙትን አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝን መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም.  በመተካት ወንበሩን የተቆጣጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ናቸው፡፡  ጠቅላይ ሚኒስትርነቱን  በያዙ በቀናት ውስጥ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ኢሕአዴግ በሕዝቡና በአገር ላይ የፈጸማቸውን ጥፋቶችና ስህተቶች በማመን ይቅርታ መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡  ከሰኔ 16 ቀን 2ዐ1ዐ ዓ.ም. ጀምሮ የተለያዩ ተግዳሮቶች የገጠማቸውም ቢሆንም፣ ይቅርታውን ተስፋ አድርገው የተከተሏቸው በአገር ውስጥም ይሁን በውጭ አገሮች የነበሩ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ ድጋፍም ሆነ ተቃውሞ ሳያሰሙ የየራሳቸውን እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል፡፡  ወደ አገር ቤትም እንደገቡ በደጋፊዎቻቸው አማካይነት በርካታ ጥፋቶች ሲፈጸሙ ኃላፊነት ወስደው ሕዝቡን ይቅርታ ከመጠየቅ ይልቅ፣ እንደ ጀብዱና ማስፈራሪያ አድርገው የወሰዱት ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ነበሩ፡፡ የእነዚህ የተወሰኑ ተፎካካሪ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ በአክራሪ አክቲቪስቶች እገዛ ያደረጉት ዘርን መሠረት ያደረገ እንቅስቃሴ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ሥልጣን ሲመጡ ያሳዩትን የዴሞክራሲ ጭላንጭል ወደ ማጥፋት ወስዶታል፡፡  በመሆኑም በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኙ ደጋፊዎች ተቃውሞአቸውን መሰንዘር ጀምረዋል፡፡ ምንም እንኳን ጥቂት የተፎካካሪ ፓርቲዎችና አክቲቪስቶች ተቃውሞአቸውን በመቀጠል የተለያዩ አላስፈላጊ ድርጊቶችን ለመፈፀም ባደረጉት እንቅስቃሴ በሰው ሕይወት፣ በሃይማኖት ተቋማትና የተለያዩ ንብረቶች ላይ የማይተካ ጉዳት ቢያደርሱም፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አልፎ አልፎ በስብሰባዎችና በጋዜጣዊ መግለጫዎች ላይ ከሚያስተላልፉት ማስጠንቀቂያና ምክር በስተቀር ዕርምጃ አልወሰዱም፡፡  ነገር ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢሕአዴግን በሚመለከት ባደረጉት ጠቅላላ ስብሰባ “ኢሕአዴግ” የሚለውን ለ31 ዓመታት የቆየውን ስያሜ ወደ ብልጽግና ፓርቲ እንዲቀየር አድርገዋል፡፡ ከሕወሓት በስተቀር ሁሉም ክልላዊ ፓርቲዎች በመደገፋቸውና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም ተመዝግቦ ዕውቅና በማግኘቱ ሥራውን ቀጥሏል፡፡ 

ፓርቲው የ2ዐ12 አገራዊ ምርጫ መደረግ አለበት በማለት ከጥቂት ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር ተመሳሳይ አቋም በመያዝ፣ አብዛኛዎቹ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ባይስማሙም ምርጫውን ነሐሴ 23 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም. ለማድረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀጠሮ ይዞ የተለያዩ የምርጫ ቁሳቁሶችን ለማሟላት ሽር ጉድ ማለት ጀምሮ ነበር፡፡  ነገር ግን መድኃኒት የለሹና ዘር፤ ቀለምና ማንነትን የማይለየው ኖብል ኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ በመከሰቱ፣ አገራዊ ምርጫ 2ዐ12 አደጋ ላይ ወድቋል፡፡  ወረርሽኙ በከፍተኛ ፍጥነት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በመግደልና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩትን የቫይረሱ ሰለባ በማድረግ ኢትዮጵያን ጨምሮ የዓለም አገሮችን ሥጋት ላይ ጥሏል፡፡  በዚህ አስጨናቂ ጊዜ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫው እንዲካሄድ ማድረግ እንደማይችል ለፓርላማው አሳውቋል፡፡

መንግሥትም ወረርሽኙን በጋራ ለመከላከል እንዲያመቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል፡፡  ይህ ሁሉ ተደምሮ ምርጫ ቦርድ ምርጫ ማድረግ እንደማይችል ያቀረበው ጥያቄ በፓርላማው ተቀባይነት በማግኘቱ፣ በቀጣይ ምን መደረግ እንዳለበት ጉዳዩን አስጠንቶ የመፍትሔ ሐሳብ እንዲያቀርብ ኃላፊነቱን ለሕግ፣ ለፍትሕና ዴሞክራሲያዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቶለት ነበር፡፡  ኮሚቴውም ያቀረበው ሐሳብ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ሕገ መንግሥቱን እንዲተረጐም የሚል ነው፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ሕገ መንግሥቱን ፌዴሬሽን ምክር ቤት እንዲተረጉም እንጂ ከወር በኋላ የምርጫ ጊዜያቸውን ስለሚያጠናቅቁት የምክር ቤት አባላትም ሆነ የገዥው መንግሥትን ዕጣ ፈንታ በሚመለከት ያለው ነገር አልነበረም፡፡  የምክር ቤቱም  የቀረበውን “ሕገ መንግሥቱ ይተርጐም” ውሳኔ በአብላጫ ድምፅ ወስኖ አሳልፏል፡፡ ሕገ መንግሥቱ በግልጽ የደነገገውን በመተላለፍ ምክር ቤቱ የሥራ ዘመኑን በሕገ ወጥ መንገድ ማራዘም እንደማይችልና ምንም የሚተረጐም ነገር እንደሌለ ከሕወሓት አባላትና አንዳንድ የተፎካከሪ ፓርቲዎች ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፎች

በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ብዛት ሥጋት ፈጥሯል

በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ብዛት ሥጋት ፈጥሯል

May 2020
ድምፃቸውን ያጠፉ ባለሀብቶች ለወገንና ለሀገር እንዲደርሱ ጥሪ ቀረበ

ድምፃቸውን ያጠፉ ባለሀብቶች ለወገንና ለሀገር እንዲደርሱ ጥሪ ቀረበ

April 2020

የአገር ውስጥ እንቅስቃሴዎችን ማስቆም ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል

April 2020

ከጥቂቶች በስተቀር ሁሉም ተከሳሾችና ታራሚዎች መፈታት አለባቸው ተባለ

April 2020

ዓለምን እያዳረሰ ያለው ኮሮና ቫይረስ ስጋትና ጭንቀት ጨምሯል

March 2020

መተግበር ሳይጀምር ሕዝቡን ያማረረው የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ

March 2020

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) እና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የቋሚ ኮሚቴውን ሐሳብ በመደገፍ ሕገ መንግሥቱ እንዲተርጐም ተስማምተዋል፡፡ ሕወሓት የትግራይ ሕዝብን ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ለማስጠበቅ እንደሚሠራ፣ ምርጫም እንደሚያካሂድና መሰል አጀንዳ ከሚያካሂዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር አብሮ ለመሥራት መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡  

ጠቅላይ ማኒስትር ዓብይ፣ ሚያዝያ 29 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ ደግሞ ተቃውሞ ያነሱትን ተፎካካሪ ፓርቲዎችና አንዳንድ “ተሰሚነት አለን” የሚሉ አክቲቪስቶችን አስጠንቅቀዋል፡፡ ስለ ሕገ መንግሥት መተርጐም በሌሎችም አገሮች ተመሳሳይ ልምድ መኖሩንና ያለውን ጥቅም፣ እንዲሁም የሽግግር መንግሥት የማያስፈልግ መሆኑን አስረድተው፣ “ሕዝብ ለአደጋ ተጋልጦ ባለበት ጊዜ ሥልጣንን ያለ ምርጫ ከሕግ አግባብ ውጭ በሁከትና ብጥብጥ ካልሰጣችሁኝ፣ አገር አተራምሳለሁ የሚለውን ማንኛውንም ኃይል አንታገስም፡፡ በቂ ዝግጅትም አለን፤” በማለት ከመስከረም 3ዐ ቀን 2ዐ13 ዓ.ም. በኋላ “ማንም አካል ሥልጣን የለውም ሁላችንም እኩል ነን፡፡  መከላከያውንም ሆነ ደኅንነቱን የሚያዝ ማንም የለም፤” በማለት የተከራከሩ አካላትን አስጠንቅቀዋል፡፡  ቀጣይ የምርጫ ሁኔታ በምን መልኩ እንደሚደረግና ከመቼ እስከ መቼ እንደሚደረግ የሚተነትነው የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ትርጉምና ዝርዝር ሁኔታ ከተገለጸ በኋላ ምን ሊያስከትል እንደሚችልም እየተጠበቀ ነው፡፡ 

Share1TweetShare

ተዛማጅ Posts

በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ብዛት ሥጋት ፈጥሯል
ምን ከበር አለ?

በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ብዛት ሥጋት ፈጥሯል

በ ሪፖርተር መጽሔት
May 2020
0

አንድ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ -19) ተጠቂዎች ቁጥር ከመቶ በላይ መድረሱ በተለይ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ ሥጋት ፈጥሯል፡፡ አብዛኛዎቹ የቫይረሱ ተጠቂዎች ከአዲስ አበባና ከሶማሌ ክልል...

ተጨማሪ ያንብቡ
ድምፃቸውን ያጠፉ ባለሀብቶች ለወገንና ለሀገር እንዲደርሱ ጥሪ ቀረበ

ድምፃቸውን ያጠፉ ባለሀብቶች ለወገንና ለሀገር እንዲደርሱ ጥሪ ቀረበ

April 2020
የአገር ውስጥ እንቅስቃሴዎችን ማስቆም ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል

የአገር ውስጥ እንቅስቃሴዎችን ማስቆም ላይ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል

April 2020
ከጥቂቶች በስተቀር ሁሉም ተከሳሾችና ታራሚዎች መፈታት አለባቸው ተባለ

ከጥቂቶች በስተቀር ሁሉም ተከሳሾችና ታራሚዎች መፈታት አለባቸው ተባለ

April 2020
ዓለምን እያዳረሰ ያለው ኮሮና ቫይረስ ስጋትና ጭንቀት ጨምሯል

ዓለምን እያዳረሰ ያለው ኮሮና ቫይረስ ስጋትና ጭንቀት ጨምሯል

March 2020
መተግበር ሳይጀምር ሕዝቡን ያማረረው የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ

መተግበር ሳይጀምር ሕዝቡን ያማረረው የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ

March 2020
Ethiopian Reporter Magazine

መፍትሔ ያልተገኘላቸው የታገቱ የደንቢዶሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች

February 2020

በብዛት በመነበብ ላይ ያሉ መጣጥፎች

ዶ/ር ቅድስት

“አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

May 2020
C:\Users\IT\Documents\A01\pics

የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

July 2020
የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

May 2020
ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

May 2020
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ

ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

May 2020

Follow us on Facebook

  • ዶ/ር ቅድስት

    “አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

    384 shares
    Share 384 Tweet 0
  • የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

    21 shares
    Share 21 Tweet 0
  • የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

    0 shares
    Share 0 Tweet 0
  • ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

    44 shares
    Share 44 Tweet 0
  • ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

    169 shares
    Share 169 Tweet 0
Ethiopian Reporter Magazine

ሪፖርተር ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር

(+251) 116 61 61 81

(+251) 116 61 61 85

[email protected]

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተመ የሚወጣ ወርኃዊ መጽሔት ሲሆን፣ የሚያተኩረውም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

ሪፖርተር መጽሔት በ ኢሜይል ለማግኘት

  • Ethiopian Reporter
  • The Reporter Ethiopia
  • Reporter Tenders
  • Ethiopian Reporter Jobs

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • የፊት ገጽ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

Login to your account below

Forgotten Password?

Fill the forms bellow to register

All fields are required. Log In

Retrieve your password

Please enter your username or email address to reset your password.

Log In