Ethiopian Reporter Magazine
Wednesday, March 29, 2023
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
Ethiopian Reporter Magazine
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
Ethiopian Reporter Magazine
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ የክፍለ አኅጉራዊው ኦሊምፒክ ፕሬዚዳንት ሆኑ

በ ሔኖክ ያሬድ
May 2021
አዲሱ የአኖካ ዞናዊ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ (ዶ/ር)

አዲሱ የአኖካ ዞናዊ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ (ዶ/ር) - (ፎቶ አኖካ)

0
ያጋሩ
280
ዕይታዎች
Share on FacebookShare on Twitter

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደጊዮርጊስ (ዶ/ር) የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር- የዞን አምስት (አኖካ ዞን 5) ፕሬዚዳንት ሆነው በከፍተኛ ድምፅ ተመረጡ፡፡

አኖካ ዞን-5 በክፍለ አኅጉሩ የሚገኙ አሥራ አንድ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎችን ከኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ግብፅ፣ ሱዳን፣ ዑጋንዳ፣ ሶማሊያ፣ ታንዛንያ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ኤርትራና ደቡብ ሱዳን ያቀፈ ነው፡፡

ዞናዊው አኖካ ቅዳሜ ሚያዝያ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. በኢንቴቤ፣ ዑጋንዳ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባዔው፣ ዶ/ር አሸብር ተፎካካሪያቸውን የግብፅን ተወካይ ኤሌሪያን ሸሪፍን ያሸነፉት በ7ለ3 የድምፅ ልዩነት መሆኑን ዴይሊ ሞኒተር ከስፍራው ዘግቧል፡፡

ሱዳናዊው ሁሳም ሆጃሊ ምክትል ፕሬዚዳንት፣ ደቡብ ሱዳናዊው ቶንግ ዴራን ዓቃቤ ነዋይ ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ለሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልነት ከተመረጡት መካከል አቶ ሉል ፍሥሓዬ (ኤርትራ) ይገኙበታል፡፡ የኬንያው ፍራንሲስ ሙቱኩ ዋና ፀሐፊ ሆነው ያለምንም ተፎካካሪ መመረጣቸውን ዘገባው አክሏል፡፡
በዞኑ የሚገኙ የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ (አይኦሲ) አባላት ያለ ውድድር በቀጥታ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ሲሆኑ፣ ከነዚሁም መካከል ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማይ ብርሃነ (ኢትዮጵያ) እና ተሰናባቹ ዑጋንዳዊው ፍሬድሪክ ብሊክ ይገኙበታል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፎች

የስፖርት ውድድሮችን ያዘጋው የኮሮና ወረርሽኝ

የስፖርት ውድድሮችን ያዘጋው የኮሮና ወረርሽኝ

April 2020
ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

March 2020

በየአራት ዓመቱ እንዲካሄድ ምክረ ሐሳብ የቀረበበት የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ

February 2020

ከሃምሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ዘንድሮ በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስሙ የነገሠው አበበ ቢቂላ

January 2020

አዲሱ ፕሬዚዳንት አሸብር ለአራት ዓመታት አኖካን ከመሩት ዑጋንዳዊው ብሊክ መንበሩን በተረከቡበት ወቅት ባሰሙት ዲስኩር፣ ‹‹እንደ ዞን ለስኬት አብረን መሥራት አለብን፡፡ በግልጽነት ለማስተዳደር ቃል እንገባለን፤›› ካሉ በኋላ ለዚህም ካለፈው አመራር ጋር እጅ ለእጅ ተያይዘው ለመሥራት ቃል መግባታቸው ዘገባው ጠቄመዋል፡፡

ተሰናባቹ የአኖካ ዞን አምስት ፕሬዚዳንት ዊሊያም ቢልክ በዘመናቸው በትጋት ማገልገላቸውን አስታውሰው፣ ‹‹ለአባላት ንቁ ተሳትፎ፣ በዞኑ የወጣት ጨዋታዎችን በማካሄድ፣ ከዞኑ ወደ ኦሊምፒክ የተጨመሩ የአትሌቶች ብዛትና ሌሎች በርካታ በመሆናቸው በሥራዬ ዘመን ብዙ ነገሮችን አሳክተናል፡፡ ለተሻለ ሥራ ሕገ ደንቡን መገምገም አለብን፤›› ተናግረዋል፡፡

‹‹ሁሉንም አሸናፊዎች እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ በአኖካ ዞን አምስት ውስጥ ለስፖርቶች ልማት ስኬት አመራሮቹ አንድ ሆነው እንዲቀጥሉ አደራ እላለሁ፤›› ያሉት የአኖካ ፕሬዚዳንት ሙስጠፋ ቢራፍ፣ የኦሊምፒክ እንቅስቃሴ እሴቶችን ለማሳካት በጋራ መሥራት እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

ለአዲሱ ኦሊምፒያድ የተምረጡት አመራሮች (ፎቶ አኖካ)
ለአዲሱ ኦሊምፒያድ የተምረጡት አመራሮች (ፎቶ አኖካ)

ኢትዮጵያና አኖካ
አምሳ አራት ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖካ)፣ ከአራት አሠርታት በፊት በናይጄሪያ ሲቋቋም ለምሥረታው ዓይነተኛ ሚና ከነበራቸው መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሱት ኢትዮጵያዊው አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ናቸው፡፡ ነፍስ ኄር ይድነቃቸው በወቅቱ የኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ኮሚቴ አባል፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንትና አህጉራዊ ኮንፌዴሬሽኖችን የሚያስተሳስረው የአፍሪካ ስፖርት ኮንፌዴሬሽኖች ማኅበር (ዩካሳ) መሥራችና ፕሬዚዳንት ስለነበሩ አኖካ ተመሥርቶ የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች በርሱ ሥር እንዲከናወንም አልመው ነበር፡፡
በሰኔ 1973ቱ የአኖካ መሥራች ጉባዔ የቶጎው አናኒ ማቲያ የመጀመርያው ፕሬዚዳንት ሆነው ሲመረጡ፣ በወቅቱ የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ፕሬዚዳንትና የስፖርት ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ጸጋው አየለ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል፡፡ አኖካ ከአራት ዓመት በኋላ የመጀመርያ ጉባዔውን በአዲስ አበባ አፍሪካ አዳራሽ ሲያካሂድ፣ አቶ ጸጋው በስፖርትና በኦሊምፒክ መድረኮች ላበረከቱት የላቀ አስተዋጽዖ፣ በኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ኮሚቴ ይሁንታ አግኝተው በወቅቱ ፕሬዚዳንት ጁዋን ኦቶንዮ ሳማራንሽ አማካይነት፣ ርእሰ ብሔር ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያም በተገኙበት የኦሊምፒክ ኦርደር ሜዳይ (the silver medal of the Olympic Order) ተሸልመዋል፡፡ ከሁለት ዓመት በኋላ ደግሞ የወርቅ ሜዳሊያ ከመሸለማቸው በተጨማሪ የአፍሪካ ስፖርት ምክር ቤት የዕድሜ ልክ አባል ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል፡፡

ከአቶ ጸጋው በመቀጠል የአኖካ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ውስጥ በ2001 ዓ.ም. የገቡት ብቸኛዋ ኢትዮጵያዊት ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማይ ናቸው፡፡ እሳቸው አኅጉራዊውንም ማኅበር አልፈው፣ በዓለም ደረጃ የተመሠረተውና የኢትዮጵያዊው ይድነቃቸው ተሰማ አሻራ ያለበት የብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖክ)፣ የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት አባል ሆነው እየሠሩ ይገኛሉ፡፡

ShareTweetShare

ተዛማጅ Posts

የስፖርት ውድድሮችን ያዘጋው የኮሮና ወረርሽኝ
ስፖርት

የስፖርት ውድድሮችን ያዘጋው የኮሮና ወረርሽኝ

በ ደረጀ ጠገናው
April 2020
0

በማይታመን ፍጥነት ዓለምን እያዳረሰ በሚገኘው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት በርካታ ስፖርቶች እንዲቋረጡ ተደርጓል፣ አንዳንዶቹ ደግሞ ለሌላ ጊዜ ተላልፏል፡፡ የኮሮና ወረርሽኝ በዓለም ዙሪያ ከ34,000 በላይ ሰዎችን ለኅልፈት ዳርጓል፡፡ ኮቪድ-19 የሚል ተቀፅላ...

ተጨማሪ ያንብቡ
ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

ፖለቲካዊ ተቃውሞን በኦሊምፒክ መድረክ ማንፀባረቅ ያገደው ድንጋጌ

March 2020
በየአራት ዓመቱ እንዲካሄድ ምክረ ሐሳብ የቀረበበት የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ

በየአራት ዓመቱ እንዲካሄድ ምክረ ሐሳብ የቀረበበት የአፍሪካ አገሮች ዋንጫ

February 2020
አበበ ቢቂላ

ከሃምሳ ስድስት ዓመታት በኋላ ዘንድሮ በሚካሄደው የቶኪዮ ኦሊምፒክ ስሙ የነገሠው አበበ ቢቂላ

January 2020

በብዛት በመነበብ ላይ ያሉ መጣጥፎች

ዶ/ር ቅድስት

“አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

May 2020
C:\Users\IT\Documents\A01\pics

የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

July 2020
የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

May 2020
ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

May 2020
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ

ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

May 2020

Follow us on Facebook

  • ዶ/ር ቅድስት

    “አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

    384 shares
    Share 384 Tweet 0
  • የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

    21 shares
    Share 21 Tweet 0
  • የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

    0 shares
    Share 0 Tweet 0
  • ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

    44 shares
    Share 44 Tweet 0
  • ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

    169 shares
    Share 169 Tweet 0
Ethiopian Reporter Magazine

ሪፖርተር ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር

(+251) 116 61 61 81

(+251) 116 61 61 85

[email protected]

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተመ የሚወጣ ወርኃዊ መጽሔት ሲሆን፣ የሚያተኩረውም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

ሪፖርተር መጽሔት በ ኢሜይል ለማግኘት

  • Ethiopian Reporter
  • The Reporter Ethiopia
  • Reporter Tenders
  • Ethiopian Reporter Jobs

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • የፊት ገጽ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

Login to your account below

Forgotten Password?

Fill the forms bellow to register

All fields are required. Log In

Retrieve your password

Please enter your username or email address to reset your password.

Log In