Ethiopian Reporter Magazine
Wednesday, March 29, 2023
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
Ethiopian Reporter Magazine
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
Ethiopian Reporter Magazine
ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ

ለአፍሪካ ነፃ አወጣጥ መንገድ ጠራጊ የሆነው የኢትዮጵያ ድል 80ኛ ዓመት

በ ሔኖክ ያሬድ
May 2021
አርበኞች ሽለላና ፉከራ ሲያሰሙ

አርበኞች ሽለላና ፉከራ ሲያሰሙ

0
ያጋሩ
737
ዕይታዎች
Share on FacebookShare on Twitter

ኢትዮጵያ በወራሪው የፋሺስት ጣሊያን ሠራዊት ላይ ድል የተቀዳጀችበት ሰማንያኛ ዓመት ረቡዕ ሚያዝያ 27 ቀን 2013 ዓ.ም. አክብራለች፡፡ በተለይ በዓሉ በአዲስ አበባ ከተማ በአራት ኪሎው የሚያዝያ 27 አደባባይ፣ የጥንት አርበኞችና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ሲከበር የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከድል ሐውልት ሥር ጉንጉን አበባ አስቀምጠዋል፡፡

በሥነ በዓሉ ላይ ‹‹ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቅኝ ያልተገዛች አገር መባሉ ትልቅ ኩራት ነው፤›› በማለት ዲስኩር ያሰሙት ምክትል ከንቲባዋ፣ ጀግኖች አርበኞች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥር በሚገኙ ሆስፒታሎች በነፃ እንዲታከሙ መወሰኑንም ገልጸዋል፡፡

ታሪካዊው ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም.፣ ፋሺስት ጣሊያን በመስከረም 1928 ዓ.ም. በወልወል በኩል የጀመረችው ወረራ አጠናክራ ለአምስት ዓመታት በወረራ ከያዘችባቸው ግዛቶች በኢትዮጵያውያን ተጋድሎና እርመኛነት በድል የተጠናቀቀበት መሆኑ ነበር፡፡

የመጨረሻው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ (1923-1967)፣ በስደትና በዲፕሎማሲያዊ ትግል ከቆዩበት የእንግሊዟ ባዝ ከተማ፣ በሱዳን በኩል በምዕራብ ኢትዮጵያ ኦሜድላ ላይ ጥር 12 ቀን 1933 ዓ.ም. የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ያውለበለቡበት ከሦስት ወራት ቆይታ በኋላም ከአርበኞች ጋር የዘለቁበትና በዕለተ ቀኑ ሚያዝያ 27 አዲስ አበባ የደረሱበት ነበር፡፡

ተዛማጅ ጽሑፎች

ምንም ይዘት የለም
የድል በዓሉ የአከባበር ገጽታ

የታሪክ ጸሐፊው አቶ ዘውዴ ረታ፣ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት በሚባለው መጽሐፋቸው ስለ ታሪካዊቷ ሚያዝያ 27 እንዲህ ጽፈዋል፡፡
‹‹ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓ.ም. ደግሞ ንጉሠ ነገሥቱ በከፍተኛ አጀብ እኩለ ቀን ስድስት ሰዓት ላይ ከታላቁ የዳግማዊ ምኒልክ ቤተ መንግሥት አደባባይ ላይ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ሰንደቅ ዓላማችንን መልሰው ሰቀሉት፡፡ የክብር ዘብ ተሰልፎ፣ በራስ አበበ አረጋይ የሚመራው አሥር ሺህ አርበኞች ያሉት ጦር ዙሪያውን በሀገር ፍቅርና በብሔራዊ ስሜት እንደቆፈጠነ፣ በሱዳን በኩል የመጣውና በሻለቃ ዊንጌት የሚመራው የጌዲዮን ጦርም ተሰልፎ፣ መድፍ ተደጋግሞ እየተተኮሰ ሰንደቃችን በክብር ከፍ አለ፡፡››

የፋሺስቶች ወረራና ለጊዜውም ቢሆን ኢትዮጵያን መያዛቸው፣ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጀመረው በአውሮፓ ውስጥ ነው ከሚለው አተያይ በተቃራኒው፣ በአፍሪካ ኢትዮጵያ ውስጥ መስከረም 22 ቀን 1928 ዓ.ም. በተፈጸመው ወረራ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጀመሩን የታሪክ ምሁራኑ ንጉሤ አየለ (ፕሮፌሰር)፣ አቶ ጥላሁን ጣሰው፣ ዓለሜ እሸቴ (ዶ/ር)፣ ሪቻርድ ፓንክረስት (ፕሮፌሰር) ሞግተዋል፡፡

ጣሊያን በዓድዋ ላይ የደረሰበትን ሽንፈት ለመበቀል ከ40 ዓመት ቆይታ በኋላ በፋሺስታዊ መንግሥቷ አማካይነት በአምስቱ ዘመን የሠራችው ግፍ ተነግሮ አያልቅም፡፡ ወረራውን በፈጸመች ባመቱ በየካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. በአዲስ አበባና በአካባቢው ከፈጸመችው ግፍ አንስቶ በሁሉም አካባቢ ብዙ አጥፍታለች፡፡ ከእነዚህም መካከል የመጀመርያው የፋሺስት ወንጀለኞች የኢትዮጵያን ሠራዊት የፈቱበት በተምቤንና በሐሸንጌ በመርዝ ጋዘ ያደረሱት እልቂት ይጠቀሳል፡፡

የታሪክ ባለሙያው አቶ ጥላሁን ጣሰው Trying Times (ትራዪንግ ታይምስ) በተሰኘው መጽሐፋቸው እንደጻፉት፣ ፋሺስት ጣሊያን በ1928 ዓ.ም. ኢትዮጵያን የወረረችው፣ በቅኝ በያዘቻቸው በሰሜን በኤርትራ በኩልና በደቡብ ምሥራቅ በኢጣሊያን ሶማሊላንድ በኩል በ400 ሺሕ ወታደሮች፣ በ300 የጦር አውሮፕላኖች፣ በ30 ሺሕ ተሽከርካሪዎችና በ400 ታንኮች አማካይነት ነበር፡፡ ሙሶሎኒ በወቅቱ የደረሰበትን ሽንፈት ለመቋቋምና ለመቀልበስ የወሰደው እርምጃ ሠራዊቱ በመርዝ ጋዝ እንዲጠቀም ማዘዙ ነው፡፡ የታኅሣሥ 18 ቀን 1928 ዓ.ም. የሙሶሎኒ ትዕዛዝ በተምቤንና በሐሸንጌ ሐይቅ ለሺዎቹ እልቂት ሰበብ ሆኗል፡፡

‹‹በተምቤን ጦርነት ጊዜ ኢትዮጵያውያን ዘመናዊ ባልሆኑ መሣርያዎች ድል አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ጦር ድል በማድረጉ ፋሺስት የኬሚካል ጥቃቱን ፈጸመ፡፡ በዚያን ጊዜ ያለቁት 700 ሺሕ የሚደርሱ ናቸው፡፡››

ከግማሽ ምዕት ዓመት በፊት በታተመ የማስታወቂያ ሚኒስቴር የታሪክ ድርሳን ላይ እንደተመለከተው፣ በነገሥታቱ መሪነት ኢትዮጵያን የድል አክሊል እንደተቀዳጀች እንድትኖር ያደረጓት ሕይወታቸውን ስለሠዉላትና የማትናድ ሕንፃና የማትፈርስ ግንብ አድርገው ስለገነቧት ነው፡፡

ትንሣኤና ሕይወት ሚያዝያ ፳፯ት በሚል ርዕስ በ1956 ዓ.ም. የታተመው መጽሐፍ የታሪክ ሥፍራዎችና ሜዳዎች፣ የነፃነት ቀኖችና ወሮች ከነዘመናቸው የማይረሱ ናቸው ይላል፡፡ ለምሳሌ ዓድዋና የካቲት 23 ቀን በመቼውም ዘመን በማናቸውም ወርና ቀን ቢሆን ሲታወሱ ትዝ የሚለው፣ በ1888 ዓ.ም. ከጣሊያኖች ጋር ተደርጎ በነበረው ጦርነት የተገኘው ድልና በዚህ ምክንያት በዓለም ላይ ጮራውን የፈነጠቀው የኢትዮጵያ የመታወቅ ዝና ነው፡፡ ድሉም ሲታሰብ አብረው ከሚታሰቡት ከንጉሠ ነገሥቱ ከዳግማዊ አፄ ምኒልክ ጀምሮ ከሠራዊት እስከ መኳንንት የነበሩት የጦር ጀግኖች ናቸው፡፡

‹‹ለአፄ ምኒልክና ለአፄ ኃይለ ሥላሴ ካሏቸው የድል ቀኖች ዋናዎቹ የካቲት 23 ቀን (1888 ዓ.ም.) እና ሚያዝያ 27 ቀን (1933 ዓ.ም.) ናቸው፡፡ ከዚህም አስቀድሞ ለነበሩት ለአፄ ዮሐንስ የድል ቀኖችና ሜዳዎች ነበሯቸው፤ እነ ጉንደት፣ ጉራዕ፣ ሰሐጢና ዶግዓሊ የየራሳቸው የድል ቀኖች አሏቸው፡፡
ከስምንት አሠርታት በፊት የተገኘው የሚያዝያ 27ቱ ድል ለመላው ለአፍሪካ ነፃ አወጣጥ መንገድ ጠራጊ መሆኑንም ያመሠጥራሉ፡፡ ለኢትዮጵያ ድጋፍ በሰጠችው የእንግሊዝ ጦር ሠራዊት ውስጥ ከቅኝ ግዛቶቿ የአፍሪካ አገሮች የተመለሱት አፍሪካውያን ወታደሮች ኅሊና ውስጥ ‹‹እኛም ነፃ መውጣት አለብን!›› የሚለው መነሳሳት የታየው በሚያዝያው ድልና ስኬት መሆኑም ተመልክቷል፡፡

እንደ ታሪካዊው ድርሳን አዘጋገብ፡ ‹‹ኢትዮጵያ ከ1928 ዓ.ም. ሚያዝያ 27 ቀን (አዲስ አበባ በፋሺስት ጣሊያን የተያዘችበት) እስከ 1933 ሚያዝያ 27 ቀን (አዲስ አበባ በድል የተያዘችበት) ድረስ የጠላት ኰቴ በመስኮቿ ላይ ቢዘዋወርም ገዢነቱን አላወቀችለትም፡፡ ጫካው ሁሉ የጃርት ወስፌ ስለሆነበትና ሜዳውም ቢሆን አቃቅማ ብቻ ሆኖ ስላስቸገረው ምን ያህል ጭንቀት እንዳደረበት አምስት ዓመት ያልሞላው የሥቃዩ ዘመን ምስክር ነው፡፡››

የድል በዓሉ የአከባበር ገጽታ

በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ከ1934 ዓ.ም. እስከ 1966 ዓ.ም. ድረስ የድሉ በዓል ይከበር የነበረው ሚያዝያ 27 ቀን ሲሆን፣ ከደርግ መንግሥት መምጣት በኋላ በዓሉን ወደ ‹‹መጋቢት 28›› ለውጦት ከወደቀም በኋላ እስከ 1987 ዓ.ም. ሲከበር ኖሯል፡፡

ኢሕአዴግ ሥልጣን ላይ በወጣ በአምስተኛ ዓመቱ በነባር አርበኞቹና በኅብረተሰቡ ጥያቄ፣ በታሪክ ምሁራንም አረጋጋጭነት በዓሉ በ1988 ዓ.ም. ወደ መሠረታዊ ቀኑ ሚያዝያ 27 ቀን ተመልሶ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡

ShareTweetShare

ተዛማጅ Posts

ምንም ይዘት የለም

በብዛት በመነበብ ላይ ያሉ መጣጥፎች

ዶ/ር ቅድስት

“አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

May 2020
C:\Users\IT\Documents\A01\pics

የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

July 2020
የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

May 2020
ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

May 2020
ነጋድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ

ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

May 2020

Follow us on Facebook

  • ዶ/ር ቅድስት

    “አንድ ሰው ምልክቱ ስላልታየበት በኮሮና ቫይረስ አልተጠቃም ብሎ መደምደም አይቻልም”

    384 shares
    Share 384 Tweet 0
  • የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውኃ ሙሌትና መቆሚያ ያጣው የግብፅ ሩጫ

    21 shares
    Share 21 Tweet 0
  • የዱር እንስሳት በአንድነት ፓርክ

    0 shares
    Share 0 Tweet 0
  • ድል አብሳሪዎቹ ጀግኖች ኢትዮጵያውያት

    44 shares
    Share 44 Tweet 0
  • ከጦር ጀግኖች ባሻገር . . .

    169 shares
    Share 169 Tweet 0
Ethiopian Reporter Magazine

ሪፖርተር ሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር

(+251) 116 61 61 81

(+251) 116 61 61 85

[email protected]

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት

የኢትዮጵያ ሪፖርተር መጽሔት በሚዲያና ኮምዩኒኬሽንስ ሴንተር እየታተመ የሚወጣ ወርኃዊ መጽሔት ሲሆን፣ የሚያተኩረውም በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

ሪፖርተር መጽሔት በ ኢሜይል ለማግኘት

  • Ethiopian Reporter
  • The Reporter Ethiopia
  • Reporter Tenders
  • Ethiopian Reporter Jobs

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

ውጤት የለም
ሁሉንም ውጤት ይመልከቱ
  • የፊት ገጽ
  • ከሪፖርተር
  • ምን ከበር አለ?
  • አንኳር
  • አደባባይ
  • ምጣኔ ሀብት
  • ማኀበረ ሰብ
  • የሕግ ነገር
  • ጥበብ እና ባህል
  • እንዴት ነው ነገሩ?
  • ሰበዝ
  • ሠገነት
  • ስፖርት

© 2020 Ethiopian Reporter Magazine - By Media And Communications Center.

Login to your account below

Forgotten Password?

Fill the forms bellow to register

All fields are required. Log In

Retrieve your password

Please enter your username or email address to reset your password.

Log In